Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

በሲስተም ችግር ምክንያት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፣ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር ባንኩ መግለጹ ይታወቃል፡፡

በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸው ይታወሳል፡፡

አሁን ላይም በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመራቸውን ነው ባንኩ ያስታወቀው፡፡

ባንኩ ደንበኞቹ በትዕግስት ስለጠበቁ አመስግኖ ፥ ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎልም ይቅርታ ጠይቋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.