የኡጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኡጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮቢናህ ናባንጃ በአዲስ አበባ የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎብኝተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ÷ ጠቅላይ ሚኒስትሯን ተቀብለው የፓርኩን አጠቃላይ እንቅስቃሴና የኩባንያዎችን የምርት ሂደት እንዳስጎበኙ የኮርፖሬሽኑ መረጃ አመልክቷል።