Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 3ኛ ወርቋን አገኘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በሴቶች 800 ሜትር ውድድር ኢትዮጵያ 3ኛ ወርቋን በፅጌ ዱጉማ አማካኝነት አግኝታለች፡፡ ፅጌ ውድድሩን በ1 ደቂቃ ከ57 ሰከንድ ከ74 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት ነው የጨረሰችው፡፡ ፅጌ ባለፈው ወር በተደረገው የአለም የቤት ውስጥ ውድድር የወርቅ ሜዳልያ ማሸነፏ ይታወሳል። ሌሎች በፍፃሜው የተሳተፉ አስቴር አሬሪ እና አዳኑ ኔንኮ በሜዳልያ ዝርዝር ውስጥ ሳይገቡ ቀርተዋል። በሰለሞን በቀለ
Read More...

ምሽት ላይ በሚከናወኑ ሁለት የፍጻሜ የሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይጠበቃሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ምሽት ላይ በሚካሄዱ የ800 ሜትር እና የ10 ሺህ ሜትር የፍጻሜ የሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተጠባቂ ናቸው፡፡ በዚሁ መሠረት የሴቶች 800 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ምሽት 4 ሠዓት ከ5 ደቂቃ ላይ የሚካሄድ ሲሆን÷ በዚሁ ዘርፍ አትሌት አስቴር አሬሬ እና ፅጌ ዱጉማ ይጠበቃሉ፡፡ እንዲሁም ምሽት 4 ሠዓት ከ35…

አትሌት ሳሙኤል ፍሬው በ3 ሺህ ሜትር መሰናከል የመጀመሪያውን ወርቅ ለሀገሩ አስገኘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ወንዶች አትሌት ሳሙኤል ፍሬው የመጀመሪያውን ወርቅ ለኢትዮጵያ አስገኝቷል፡፡ አትሌት ሳሙኤል ርቀቱን 8 ደቂቃ 24 ሰከንድ ከ30 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነው፡፡ በመርሐ ግብሩ የ5 ሺህ ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ውድድር ሲካሄድ ኢትዮጵያውያን…

ኖቲንግሃም ፎረስት 4 ነጥብ ተቀነሰበት

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኖቲንግሃም ፎረስት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን የፋይናንሺያል ጨዋነት ሕግ ተላልፏል በሚል አራት ነጥብ ተቀነሰበት፡፡ ቡድኑ ሕጉን በመተላለፍ ፕሪሚየር ሊጉ ትርፋማ እንዳይሆን ማድረጉም በገለልተኛ አጣሪ ተረጋግጧል ነው የተባለው፡፡ ይህን ተከትሎም ቡድኑ አራት ነጥብ ተቀንሶበት ነጥቡ ከ25 ወደ 21 ዝቅ ብሏል፡፡…

በቱርክ እግር ኳስ የሚስተዋሉ የሜዳ ላይ እረብሻዎች…

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራብዞን ስፖርት ደጋፊዎች የፌነርባቼ ተጫዋቾችን በጨዋታው ማጠናቀቂያ መደባደባቸውን ተከትሎ የቱርክ ሱፐር ሊግ ሌላ አሳዛኝ ክስተት አስተናግዷል፡፡ ትላንት ምሽት በፓፓራ ፓርክ የተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ተመጣጣኝ ፉክክርን አስተናግዶ በፌነርባቼ 3 ለ 2 አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ በ87ኛው ደቂቃ ላይ የተለያዩ…

ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና 2 አቻ ተለያይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አስራ ስምንተኛ ሳምንት ጨዋታ በድሬዳዋ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡ ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና ቀን 10 ሰዓት ላይ ባደረጉት ጨዋታ 2 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ በዚህም የፋሲል ከነማን ጎሎች…

አትሌት ጀማል ይመር የራሱን ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኮሪያ በተካሄደው የሴዑል ማራቶን አትሌት ጀማል ይመር የራሱን ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸንፏል፡፡ አትሌት ጀማል ውድድሩን ያሸነፈው 2 ሰዓት ከ 6 ደቂቃ ከ8 ሰከንድ በመግባት ሲሆን÷ ይህም የግሉ ፈጣን ሠዓት ሆኖ ተመዝገቧል፡፡