Fana: At a Speed of Life!

ሕንድ ለገቢ ንግድ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገሯ የመገበያያ ገንዘብ ክፍያ ፈጸመች

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሕንድ ከተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ለገዛችው ድፍድፍ ነዳጅ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገሯ የመገበያያ ገንዘብ ሩፒ ክፍያ መፈጸሟ ተሰምቷል፡፡

የዓለማችን ሦስተኛዋ የኃይል ተጠቃሚ ሀገር የገቢ ንግድ ክፍያዋን በሩፒ መፈጸሟ ገንዘቧን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ እንደሚያስችላት ተገልጿል፡፡

ሕንድ አሁን እያስተዋወቀች ያለችው ሥልት የነዳጅ አቅራቢዎችን ለማብዛት እና የውጭ ምንዛሬ ወጪዋን ለመቀነስ የያዘችው ሰፊ ዕቅድ አካል መሆኑን ቢዝነስ ስታንዳርድ ዘግቧል፡፡

ይህ የግብይት ሥርዓትም ቀደም ሲል የሕንድ ቁጠባ ባንክ አስመጪ እና ላኪዎች ክፍያቸውን በሀገሪቱ መገበያያ ገንዘብ እንዲፈፅሙ ከሚፈቅደው ውሳኔ ጋር የሚሄድ መሆኑም ነው የተመላከተው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.