Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከኮሞሮስ አቻው ጋር ነገ የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከኮሞሮስ አቻው ጋር ነገ የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያደርግ ተገለጸ። የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ 10 ሺህ 725 ተመልካቾች በሚያስተናግደው “ስታድ ኦምኒስፖርትስ ደ ማሉንዚ” ይካሄዳል። በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለጨዋታው ዝግጅት ይረዳው ዘንድ ለ30 ተጫዋቾች ጥሪ አድርጎ የነበረ ቢሆንም፣ ጥሪ ካደረገላቸው ስድሥቱን በመቀነስ 23 ተጨዋቾችን ይዞ ወደ ኮሞሮስ ማቅናቱን ኢዜአ አመልክቷል።…
Read More...

51ኛው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የፊታችን መጋቢት 19 ጀምሮ በሃዋሳ ይካሄዳል

  አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 19 እስከ 24 ቀን 2014 ዓ.ም በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማ እንደሚካሄድ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።   በሻምፒዮናው ላይ የክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮች፣ የክለቦችና በአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከላት የሚገኙ አትሌቶች ይሳተፋሉ ተብሏል።…

በቤልግሬድ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ። የልዑካን ቡድኑ ዛሬ ጠዋት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስም የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት  አትሌት ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ…

የኢትዮጵያ የወንዶች የቮሊቦል ጥሎ ማለፍ ውድድር መጋቢት 15 ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ የወንዶች የቮሊቦል ጥሎ ማለፍ ውድድር መጋቢት 15 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አስታወቀ። በአዲስ አበባ ትንሿ ስታዲየም በሚካሄደው ውድድር ወላይታ ዲቻ፣ ሙገር ሲሚንቶ፣ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ብሔራዊ አልኮል፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ መከላከያ እና…

የቤልግሬድ 2022 የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮናን ኢትዮጵያ ከአለም አንደኛ በመሆን አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣መጋቢት 12፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤልግሬድ 2022 የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮናን ኢትዮጵያ በ9 ሜዳሊያ ከአለም አንደኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቃለች፡፡ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ የሩጫ ዓይነቶች በሁለቱም ፆታ 4 ወርቅ፣ 3 ብር እና 2 ነሃስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው ማምጣት ችለዋል፡፡ ይህ ውጤትም የኢትዮጵያ ከፍተኛው የአለም የቤት…

በዓለም የቤት ውስጥ የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያ 4ኛ የወርቅ ሜዳሊያዋን በሳሙኤል ተፈራ አግኝታለች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤልግሬድ 2022 የዓለም የቤት ውስጥ የሩጫ ውድድር በመጨረሻው ቀን ከምሽቱ 2፡35 ላይ በተካሄደው የ1 ሺህ 500 ሜትር የወንዶች ፍፃሜ ሩጫ ሳሙኤል ተፈራ አንደኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል። ቀደም ብሎ በተካሄደ የ800 ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ሩጫ ፍረወይኒ ኃይሉ 2ኛ በመሆን የብር…

ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያው ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አንደኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር ተጫውቷል፡፡ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ከዩጋንዳ አቻቸው ጋር አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሜዳው ውጭ ባስቆጠራቸው ሁለት ጎሎች በዓለም ዋንጫ…