Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ልዕሊ ውልቀ ሰባትን ትካላትን ኢያ – ቀ/ሚ ኣቢይ ኣሕመድ

ኣዲስ ኣበባ፣ 22 ጥሪ፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ ልዕሊ ውልቀ ሰባትን ትካላትን ከምዝኾነት ቀዳማይ ሚኒስትር ፌዴሪኢ ዶክተር ኣቢይ ኣሕመድ ገሊፀፆም።

እቶም ቀዳማይ ሚኒስትር ኣብ ማሕበራዊ ሚዲያ ፌስቡክ ገፆም ኣብ ዘመሓላለፉዎ መልእኽቲ፥ “ኢትዮጵያ ዓባይ ሃገር ስለዝኾነት ሓሳብና፣ ስራሕናን ዘረባናን ኩሉ ንዕቤታ ዝምጥን ክኸውን ይግባእ፤ እንተዘይኮይኑ ግና ብሚዛን ኢትዮጵያ ተመዚንና ክንቀልል ኢና” ኢሎም።

“ኢትዮጵያ መዚና ዓቢዪ ምዃኑ ዝመስከረትሉ ኣካል ዝኾነ ይኹን ሰብ ኣየቕልሎን፤ ኢትዮያ ዘቕለለቶ ድማ ዝኾነ ይኹን ሰብ ኣየኽብዶን ታሪኽና እውን ምስክር ኢዩ” ኢሎም።

ኢትዮጵያ ዓባይ ሃገር ኢያ እንትበሃል ካብ ዜጋታታ፣ መራሕታ፣ ዓቢዪ ተጋድሎ ፈፂምና ካብ ዝብሉ ሰባት ኩሎም ንላዕሊ ዓባይ ኢያ ማለት ከምዝኾነ ዝገለፁ እቶም ቀዳማይ ሚኒስትር፥ ኣብ ዝኾነ ይኹን ዓውዲ ዘለዉ ሊቃውንቲ፣ ዝኾነ ይኹን ቅዱስ ዛዕባ ተሸኪሞም ዝተጣየሹ ትካላት፣ ሓሰባትን ርእዮተ ዓለማትን ኩሎም ትሕቲ ኢትዮጵያ ከምዝኾኑ ኣብሪሆም።

ኢትዮጵያ ድምር ውፅኢት ንኣሽሓት ዘበናት ሰሪሖምን ተጋዲሎምን ዝሓለፉ መራሕቲን ዜጋታትን ኢያ እውን ኢሎም።

ውልቀ ሰባት ንሃገር ዘይነዓቕ ኣስተዋፅኦ ዘለዎም ይኹን እምበር ህልውና ኢትዮጵያ ግን ብውልቀ ሰባት ከምዘይውሰን ኢዮም ዝገለፁ።

“ውልቀ ሰባት ንኽብሪ ሃገር ክብሉ ደሞም ኣፍሲሶም፣ ኣዕፅምቶም ኣርጊፎም፣ መስዋእቲ ከፊሎም ክትቅፅል ይውስኑ ይኾኑ እምበር፤ ንውልቀ ሰባት ተባሂሉ ሃገር ክትመውት ወይ ድማ ንኽነብር ናብ ድርድር ኣጥትቐርብን” ኢሎም።

ኢትዮጵያ በታሪኳ ብዙ ታላላቅ ጀግኖች ነበሯት

ኢትዮጵያ ኣብ ታሪኻ ብዙሓት ዓበይቲ ጀጋኑ ነይሮምዋ ዝበሉ እቶም ቀዳማይ ሚኒስትር፥ “ኢትዮጵያ ነዓና እምበር ንሕና ንኢትዮጵያ ኣይፈጠርናያን” ክብሉ ገሊፆም።

ናይና ግደ እውን ቀዳሞት ኣቦታትና ዝጀመሩዎ ፅቡቕ ተግባር ኣማዕቢልናን ኣስተኻኺልናን ንመፃኢ ወለዶ ምቕባል ኢዩ፤ ድሕሬና ዝመፅእ ወለዶ ድማ እቲ ቅብብል ተረኪቡ ንሕና ዝጀመርናዮ እናጠናኸረ ክቕፅል ኢዩ ክብሉ ኣብ መልእኽቶም ፅሒፎም።

ዓቢዪ ግድብ ህዳሰ ከም ኣብነት እንተተወሲዱ ኢትዮጵያ ካብ ትኾርዐሎም ወሰንቲ ፕሮጀክታት ሓደ ኢዩ ዝበሉ ዶክተር ኣቢይ፥ ነቲ ፕሮጀክት ዝጀመሩ መራሕቲ ይሕለፉ እመበር ህዝቢን መንግስቲን ግን እናሃነፁዎ ከምዝርከቡ ኣብሪሆም።

“ኮነ ኢልና ፅቡቕ ተግባራተር ዋና እንተሓባእና ኣብ ከይዲ ግዘ ምቕልዑ ኣይተርፍን፤ ብኣንፃሩ ድማ ንሕና ኣብ ዘለናሉ እዋን ዘግዘፍናዮ ረብሓ ዘይብሉ እንተኾይኑ ግዚኡ ሓሊዩ ክድርበ ኢዩ፤ ስለዝኾነ ንኢትዮጵያ እንትንሃንፅ አእዚ ሓቂ ክንግንዘብ ይግባእ” ክብሉ ኣተሓሳሲቦም፡፡

ቀዳማይ ሚኒስትር ኣቢይ ዘመሓላለፉዎ መልእኽቲ ሙሉእ ትሕዝቱኡ ከምዚ ዝስዕብ ብቋንቋ ኣምሓርኛ ቀሪቡ ኣሎ፦

የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች

ክቡራትና ክቡራን

ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር ናት። ሐሳባችን፣ ሥራችንና ንግግራችን ሁሉ ታላቅነቷን የሚመጥን መሆን ቢችል መልካም ነው። ካልሆነ በኢትዮጵያ ሚዛን ተመዝነን እንቀልላለን።

ኢትዮጵያ መዝና ታላቅነቱን የመሰከረችለትን ማንም አያቀልለውም። ኢትዮጵያ ያቀለለችውንም ማንም አያከብደውም። ታሪካችን ይሄንን ይመሰክራል፤ ዛሬም እየመሰከረ ነው።

ኢትዮጵያ ታላቅ ናት ስንል ከዜጎቿም፣ ከመሪዎቿም፤ ታላቅ ገድል ፈጽመናል ከሚሉ ሰዎች ሁሉ በላይ ታላቅ ናት ማለታችን ነው። በየትኛውም ዘርፍ ያሉ ልሂቃን፣ የትኛውንም የተቀደሰ አጀንዳ አንግበው የተመሠረቱ ድርጅቶች፣ ሐሳብና ርዕዮተ ዓለሞች ሁሉም ከኢትዮጵያ በታች ናቸው።

ኢትዮጵያ በሺዎች ዘመናት ሠርተውና ተጋድለው ያለፉ መሪዎችና ዜጎች ድምር ውጤት ናት።

ኢትዮጵያ – ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ ሰፍተውና መልተው የሚኖሩ፣ የሚሠሩና የሚጋደሉ ልዩ ልዩ ሕዝቦች ውጤት ናት። ታሪክ ያልመዘገባቸው፣ የታሪክ ድርሳናት የማያውቋቸው እልፍ አእላፍ ታሪክ ሠሪዎች በደምና በአጥንት፣ በላብና በወዝ በጽኑዕ መሠረት ላይ የገነቧት ሀገር ናት።

ግለሰቦች ለኢትዮጵያ የማይናቅ አስተዋጽዖ ያደርጋሉ፤ የኢትዮጵያ ህልውና ግን በግለሰቦች አይወሰንም። ግለሰቦች ለክብሯ ሲሉ ደማቸውን ሊያፈስሱ፣ አጥንታቸውን ሊከሰክሱ፣ መስዕዋት ሆነው ሊያስቀጥሏት ይወስኑ ይሆናል፤ ነገር ግን “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” እንዳለችው የቤት እንስሳ፥ ለግለሰቦች ሲባል ሀገር እንድትሞት ወይም እንድትኖር ለድርድር አትቀርብም።

ኢትዮጵያ በታሪኳ ብዙ ታላላቅ ጀግኖች ነበሯት። በየጦር ሜዳው ታላላቅ ጀብዱ የፈጸሙ አርበኞች፣ በየእውቀት መስኩ አርቀውና አስፍተው የተመለከቱ አሰላሳዮች፣ በየውድድር ሜዳው አይበገሬነታቸውን ያስመሰከሩ ተፋላሚዎች፣ በሌሎችም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች አንቱታን ያተረፉ መሪዎች ከማህጸኗ በቅለዋል፤ ወደፊትም ይበቅላሉ። ኢትዮጵያ እኛን እንጂ፣ እኛ ኢትዮጵያን አልፈጠርናትም።

እኛ ከመፈጠራችን በፊት ኖራለች፤ ከእኛ መሐል አንዳችን ስለጎደልን አትጠፋም። እኛ በዘመናት መካከል ከመጡ አርበኞች፣ አሰላሳዮች፣ ተፋላሚዎችና መሪዎች እንደ አንዱ ነን። በተሰጠን እድሜ የየበኩላችንን ጡብ አስቀምጠን እንሄዳለን።

መጭውም የአቅሙን አክሎበት ይቀጥላል። በየትውልዱ አያሌ ዜጎችን እያፈራች መገስገሷን ትቀጥላለች። የትውልድ ቅብብሎሽ ኢትዮጵያን “ኢትዮጵያ” እያደረጋት ወደፊት ትጓዛለች።

የእኛ ሚና ቀደምቶቻችን የጀመሩትን መልካም ተግባር አጎልብተንና አሳምረን ለመጪው ትውልድ ማቀበል ነው። ከእኛ በኋላ የሚመጣውም ቅብብሎሹን ቀጥሎ፣ እኛ የጀመርነውን እያጎለበተ ያስቀጥላል።

የሕዳሴ ግድብን ብንወስድ ኢትዮጵያ ከምትኮራባቸው ወሳኝ ፕሮጀክት አንዱ ነው።

ያስጀመሩት መሪዎች ቢያልፉም ሕዝብና መንግሥት እየገነቡት ይገኛል። ሌሎችም የተጀመሩ የመንገድ፣ የኢንዱስትሪ ፓርክ፣ የመስኖ ግድብ፣ የኃይል ፕሮጀክቶችን ሕዝብና መንግሥት ካለፉት ተረክቦ አስቀጥሏቸዋል። ማን ጀመረው ከሚል ይልቅ ለኢትዮጵያ ምን ጥቅም ያስገኛል በሚል እየተፈተሸ መልካም የሆነው ሁሉ ጎልብቶ ይሻገራል፤ መልካም ሆኖ ያልተገኘውም ማንም ቢሠራው ጊዜ ራሱ ጥሎት ያልፋል። የትኛውም ሀገር ከስልጣኔ ማማ ላይ የተቆናጠጠው በዚህ መልኩ ነው፤ ሌላ ተዓምር የለም። ሆን ብለን በክፋት ጥሩ ጥሩውን ብንደብቀው በጊዜ ሂደት መገለጡ አይቀርም፤ በተቃራኒው እኛ እስካለን በሚል ያገዘፍነው ጥቅም ሲታጣበት ጊዜውን ጠብቆ ይጣላል። ኢትዮጵያን ስንገነባ ይሄንን ሀቅ መገንዘብ ይገባናል፡፡

ውድ ኢትዮጵያውያን፣

መሪነት በአንድ በኩል ኃላፊነት ለመውሰድ የመቻል፣ በሌላ በኩል በፖለቲካ ትግል ውስጥ የማለፍ፣ አለፍ ሲልም የዕድል ጉዳይ ነው። ሌሎችም ዕድሉ ሲገጥማቸው፣ የፖለቲካው ሂደት ለዚያ ሲያደርሳቸውና ኃላፊነቱን ለመውሰድ ፍላጎትና ቆራጥነት ሲኖራቸው መሪ የማይሆኑበት ምንም ምክንያት የለም።

እየመሠረትነው ያለነው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሪነት የፖለቲካ ሂደት ውጤት እንዲሆን የሚያደርግ ነው። የሀገሪቱ ሕግ የሚጠይቀውን ያሟላ፤ በምርጫ ያሸነፈና በፖለቲካ ሥርዓታችን ፍኖት የተጓዘ ኢትዮጵያዊ ሁሉ መሪ ሊሆን የሚችልበትን መንገድ የሚጠርግ ነው። መሪነት ሥልጣን ሳይሆን ኃላፊነት፤ ገዥነት ሳይሆን አገልጋይነት፤ ድሎት ሳይሆን መሥዋዕትነት ነው።

መሪ ከብዙ ኢትዮጵያውያን መካከል ሕግ እና የፖለቲካ ሥርዓቱ ዕድሉን የሰጠው አንድ ወሳኝ ሰው ነው። መሪዎችን ከዚህ በላይ አድርጎ መመልከት መሪዎችንም ኢትዮጵያንም ይጎዳል። ለመሪዎች ማሰብ፣ ለመሪዎች መጨነቅም መልካምና ተገቢ ነገር ነው። መሪዎችን ከኢትዮጵያ በላይ አድርጎ መመልከት ግን ስሕተት ነው።

ኢትዮጵያ ወደረኞቿን በብዙ ግንባሮች ድል ነስታለች። ለግላዊና ድርጅታዊ ጥቅማቸው ሲሉ ሊያጠፏት የተነሱት ሁሉም አሁን ተረት ሆነዋል። ከታሪክ የማይማሩ ሰዎች ዛሬም ሆነ ወደፊት መነሳታቸው አይቀርም፤ ዳሩ ግን እንደቀደሙት እብሪተኞች ተረስተው ይቀራሉ። በሚታየውም በማይታየውም ዘመቻ ሀገራችን ድል እያደረገቻቸው ትቀጥላለች። ያኔ ጠላቶቿ የሚቀራቸው ግንባር የውሸት ግንባር ብቻ ይሆናል። በእርግጥ ዘመኑም በተወሰነ ሳይረዳቸው አልቀረም።

ዐይናቸው እያየ ልባቸው በሐሰት ፕሮፓጋንዳ የሚዋልልባቸው ሰዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ጥንት ‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው› ይባል ነበር። አሁን ‹ጦር ከፈታው ውሸት የፈታው› ሆኗል። የውሸት ፋብሪካ ከፍተው፣ ውሸት እያመረቱና ውሸት እያሸጉ፣ በጅምላና በችርቻሮ ውሸት ሲያከፋፍሉ የሚውሉ የኢትዮጵያ የጎን ውጋቶች በዝተዋል። ዓላማቸው በሌሎች ግንባሮች ያጡትን ድል በውሸት ግንባር ለማግኘት፤ እግረ መንገዳቸውንም ትርፍራፊ ገንዘብ ለመሰብሰብ ነው።

ለኢትዮጵያ መሞት የማይገኝ ዕድል መሆኑ እንደማይገባቸው ሁሉ፣ ኢትዮጵያን ለመግደል መነሣት የመጨረሻው ርግማን እንደሆነ አያውቁም። ሞት እንደሆን የማይቀር የሰው ልጅ እዳ ነው፤ ከሆነ አይቀር ለታላቋ ሀገር ለኢትዮጵያ ቢከፈል ትልቅ ክብር ነው። ኢትዮጵያ የተገነባችው በኢትዮጵያውያን ሥራ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያውያን መሥዋዕትነትም ጭምር ነው። የሐሰት አበጋዞች በሕይወት ያሉትን ገድለው የሞቱትን ሲያኖሩ ከርመዋል። ነገም አመል ነውና መቀጠላቸው አይቀርም። ኢትዮጵያውያን ግን የሚያዋጣን ለእውነት ስንል መኖር፣ በእውነት መንገድ መመላለስ እና እኛው ራሳችን እውነተኛ ሆነን መቆየት ነው።

የሐሰት ፋብሪካ በጅምላና በችርቻሮ የሚያቀርብልንን የውሸት ፕሮፓጋንዳ በሌለን ጊዜና ገንዘብ እየሸመትን፣ ስንወዛገብ በከንቱ የምንውልበት ሁኔታ ላይ አይደለንም። እንደ ሀገር ብዙ የቤት ሥራዎች አሉብን። መፈታት የሚገባቸው ቋጠሮዎች፣ መደፈን ያለባቸው ቀዳዳዎች፣ መሞላት የሚገባቸው ጉድጓዶች፣ መጠገን የሚገባቸው ድልድዮች፣ መገንባት የሚገባቸው ሥርዓቶች ተቆጥረው አያልቁም። ያለንን ውድ ጊዜና ሀብት ኢትዮጵያን ለመለወጥ፣ ኢትዮጵያን ለማበልጸግ፣ ኢትዮጵያን ለማስከበር እና ኢትዮጵያን ከፍ ለማድረግ ብናውለው ይበጃል። ከዚህ የተሻለ ገንዘብና ጊዜያችንን ሊወስድ የሚገባው ምንም ጉዳይ የለንም።

የኢትዮጵያን ወንዞች ለማልማት እኛው ራሳችን የመስኖ ቦዮችን እንቅደድ እንጂ በተቀደደልን የወሬ ቦይ አንፍሰስ። ታላቋን ሀገር በታላላቅ ሐሳቦች ይበልጥ እናተልቃት እንጂ፤ በሐሳብ አንሰን፣ በወሬ ኮስሰን ሀገራችንን አናኮስሳት። ኢትዮጵያ መግዘፍ እንጂ አንሳ መገኘት አይመጥናትም። ለዚያም ሁላችንም በየተሠማራንበት ዘርፍ በዋዛ ፈዛዛ እንቁ ጊዜያችን ማባከኑን ትተን የሰለጠነችና ለሌሎች አርዓያ መሆን የምትችል ኢትዮጵያን ገንብተን ለልጅ ልጆቻችን እናውርስ!!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትሩር!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ጥር 22፣ 2013 ዓ.ም

እዋናዊን ሓዱሽን ሓበሬታ ንምርካብ

ቴሌግራም ገፅና https://t.me/tigrignafana

ድረ ገፅና https://www.fanabc.com/tigrigna/

ትዊተር ገፅና https://twitter.com/fanatelevision

ዩቲዩብ ቻናል FBC Tigrigna

https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ሰብስክራይብ

ይግበሩ/ራ!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.